ዶ/ር ጀማል አባፊጣ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነዉ ተመረጡ

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለፕሬዝዳንትነት ቦታ ብቃቱና ፍላጎት ያላቸዉ አመልካቾች እንዲወዳደሩ ጥር 24/2011 ዓ.ም በተለያዩ ሚዲያዎች ባወጣዉ ግልጽ ማስታወቅያ መሰረት አመልካቾች መረጃቸዉን በማስገባት በተለያዩ ደረጃዎች ዉድድር ሲካሄድ ቆየቱ ይታወሳል::

በምርጫ ሂደቱም ከ250 በላይ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የዩቨርሲቲዉ ሴኔት  እና የስራ አመራር ቦርድ በቀን 01/07/2011 ዓ.ም. የቃለ-መጠይቅ ፓናል በማካሄድ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት የተወዳደሩና ማጣሪያዎችን አልፈው የደረሱ 9 እጩዎችን በመገምገም 5 እጩዎችን ለዩሲቲዉ የስራ አመራር ቦርድ አስተላልፏል፡፡ የዉድድሩ ሂደት የተመራዉ የሳይንስና ከፍተኛ ት/ት ሚኒስቴር ባወጣዉ መስፈርት ሲሆን ሂደቱን ለመምራት አምስት ሰዎችን የያዘ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየደረጃዉ ግምገማ ሲያካሄድ ቆይቷል፡፡ ኮሚቴዉ ከቦርድ አባላት፣ ከሴኔት አባላት፣ ከተማሪ፣ ከመምህራን እና ከአስተዳደር ሰራተኞች ተወካይ የተዉጣጣ ሲሆን የዉድድር ማስታወቂያ ከማዉጣት ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲዉ የስራ አመራር ቦርድ ጉባኤ የሂደቱን ዉጤት እስከ ማሳወቅ ድረስ በትጋት ሲሰራ ቆይቷል፡፡ 

 

በዚሁ መሰረት የዩኒቨርሲቲዉ የስራ አመራር ቦርድ ሚያዚያ 02/2011 ዓ.ም ባካሔደው ልዩ ጉባኤ 3 እጩዎችን (ዶ/ር ጀማባፊ፣ ፕሮፌሰር ርጋዉ ምበሉ እና ዶ/ር ናቃቸዉ ባሹን) በእጩነት ለሳይንስና ክፍተኛ ት/ት ሚኒስቴር ኣቅርቧል:: ሳይንስና ክፍተኛ ት/ት ሚኒስቴርም ዶ/ር ጀማል ባፊሚያዚያ 11/2011 ዓ ም ጀምሮ አዲሱ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነዉ እንዲያገለግሉ መርጧቸዋል፡፡  

ዶ/ር ጀማባፊጣ የዩኒቨርሲቲዉ ነባር መምህር እና ተመራማሪ ሲሆኑ በተለያዩ ደረጃዎች በዩኒቨርሲቲውና ከዩኒቨርሲቲው ውጭ በሃላፊነት ያገለገሉና በአሁኑም ወቅት የማህበረሰገልግሎት ቢሮ ዳይሬክተር ሆነዉ እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡  

የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ ዶ/ር ጀማባፊጣ ለዚህ ሃላፊነት በመመረጥዎ የተሰማዉን ልባዊ ደስታ እየገለጸ መልካም የስራና የስኬት ዘመን እንዲሆንልዎ ይመኛል፡፡

ስለ ዶ/ር ጀማባፊጣ የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልምድ ይህን አገናኝ በመጫን ሙሉ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡ 

ሚያዚያ 11/2011 ዓ.ም

ጅማ ዩኒቨርሲቲ